የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስፖርት አካዳሚ የታዳጊ ህጻናት ሳመር ካምፕ የመዝጊያ መርሃ ግብር በደመቀ ሁኔታ ተካሄደ

Peda Campus

06 Sep, 2026

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስፖርት አካዳሚ ለሁለት ወራት በተለያዩ የስፖርት ዘርፎች ሲያሰለጥናቸው የቆየውን 753 ታዳጊ ህጻናት የሳመር ካምፕ ስልጠና የመዝጊያ ስነ-ስርዓት ወላጆች፣ ዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ እና እንግዶች በተገኙበት በደመቀ ሁኔታ ተካሂዷል።

kids

BDU Sport Academy Summer Sports camp 2026 in training time

በመርሃ ግብሩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ስፖርት አካዳሚ ዲን አቶ ሲሳይ አዱኛ፣ የሳመር የስፖርት መርሃ ግብሩ ታዳጊዎች አካላዊ እድገታቸውን እንዲያሻሽሉ፣ የስፖርት ክህሎታቸውን እንዲያጎለብቱ፣ በቡድን የመስራት ባህላቸውን እንዲጠናከር እና ክረምቱን በጤናማና አስደሳች መንገድ እንዲያሳልፉ አስተዋፅኦ ማድረጉን ገልጸዋል። በተጨማሪም ልጆች ለዲጂታል ዓለም አሉታዊ ተጽዕኖዎች ተጋላጭ እንዳይሆኑ ትልቅ ሚና መጫወቱን ጠቁመዋል።

አቶ ሲሳይ አክለውም፣ በመርሃ ግብሩ የተሳተፉ ህጻናት ደስተኛ፣ ጤናማ እና በራሳቸው የሚተማመኑ እንዲሁም አዳዲስ ጓደኞችን አፍርተው ወደ መደበኛ ትምህርት ቤታቸው ከፍ ባለ ተነሳሽነት የሚመለሱ እንደሆነ ገልጸዋል።

ስፖርት አካዳሚው በበጋ ወራት 236 ታዳጊዎችን በእግር ኳስና በአትሌቲክስ ማሰልጠኑን ጠቅሰው፣ በዚህ ዓመት በዋናው ግቢ 480 እና በዘንዘልማ ግቢ 37 ታዳጊዎች በተለያዩ የስፖርት ዘርፎች ስልጠና ማግኘታቸውን ገልጸዋል። በአጠቃላይ 753 ታዳጊዎች እንደየ እድሜአቸው ተመጣጣኝ ስልጠና እንዳገኙም አመልክተዋል።

summer camp graduates

Summer Sports Camp  2026 graduates

ከሰለጠኑት ህጻናት መካከል ተሰጥኦና ፍላጎት ያላቸው በልዩ መርሃ ግብር ተመርጠው ከሰኞ እስከ አርብ ከትምህርት በኋላ እንዲሁም ቅዳሜና እሁድ በቀጣይ ስልጠና እንደሚሳተፉ ተገልጿል።

የአካዳሚው ዲን ስኬታማ የሆነው የሳመር ካምፕ መርሃ ግብር በአሰልጣኞች፣ በአስተባባሪ ኮሚቴዎች፣ እንዲሁም በወላጆች ትብብር መሳካቱን ገልጸው፣ ልጆቻቸውን በእምነት ለአካዳሚው ለሰጡ ወላጆች ልባዊ ምስጋና አቅርበዋል።

summer camp coaches

summer sports camp 2026 coaches

በእለቱም ታዳጊ ህጻናቱ በተለያዩ የስፖርት ዘርፎች ያገኙትን ክህሎትና ብቃት በአስደናቂ የስፖርት ትርኢቶች ለታዳሚዎች በማቅረብ የመዝጊያ መርሃ ግብሩን አድምቀውታል።

Center of Execelence

which are the 1st of their type in Ethiopia and/or Eastern Africa

View All Courses