Outreach News

BDU STEM Incubation center provide a laboratory training for six  school science teachers on January 13, 2024. In the Training 18 teachers  who teaches from grade 9 to grade 11 is given in Scienec subjects::(Physics,Cchemistry, and Biollogy. The session will be given for six week in weekends.

About 120 students from BDU STEM Center took part in National Math Olympiad in the first round. In the second round 71 students took the exam and 12 students passed for the final math olympiad. The final national math olympiad will be held on January 13, 2024 from 8:30 AM to 12:30PM.

የባሕር ዳር ከተማን የዲጂታል አድራሻ ስርዓት ለመዘርጋት እንቅስቃሴ ተጀምሯል።

የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፖሻል ኢንስቲትዩት የባሕር ዳር  ከተማን የዲጂታል አድራሻ ስርዓት ለመዘርጋት ከከተማ አስተዳደሩ እና ከባሕር ዳር  ዩኒቨርሲቲ ተወካዮች ጋር ተወያይቷል።

በውይይቱ የዲጂታል አድራሻ ስርዓት ፕሮጀክቱ ተግባራዊ መደረግ የከተማዋን የቱሪዝም ሃብት በቀላሉ ተደራሽ ለማድረግ እና ከቱሪዝም የሚገኘውን ገቢ ለማሳደግ እንዲሁም የዲጂታል ኢኮኖሚውን በማነቃቃትና በመገንባት ከተማዋን ለኢንቨስትመንት ምቹና ተመራጭ ለማድረግ ከፍተኛ ሚና እንዳለው ተገልጿል።

የከተማዋን የዲጂታል አድራሻ ስርአት ለመገንባት በከተማዋ የሚገኙ መኖርያ ቤቶች እና ተቋማትን ፣የመንገድና ትራንስፖርት ፍሰት መረጃን ለመተንተን ፣የዲጂታል አድራሻ ካርታን እና ሲስተምን ለመዘርጋት፣ የንግድ ተቋማት መገኛና አቅጣጫ ጠቋሚን በዲጂታል ለማገዝ፣የመሬት አስተዳደር እና ሌሎች የከተማዋን መረጃዎች ለማዘመን እንደሚረዳ ተነስቷል።

የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ በላቸው ጽሐይ የባሕር ዳር  ከተማ አስተዳደር እና ዩኒቨርሲቲ የከተማዋን የዲጂታል አድራሻ ስርአት ለመገንባት ያሳዩትን ፍላጎት እና በዘርፉ ያሉ ጅምሮችን አድንቀው የዲጂታል አድራሻ ስርአት የሀገርን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ ውጤታማ ለማድረግ ያለውን ሚና አብራርተዋል።

የባሕር ዳር  ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ አስሜ ብርሌ የፕሮጀክቱ መተግበር የከተማውን ማህበረሰብ ኢኮኖሚያዋ እና ማህበራዊ እንቅስቃሴ ለማቅለል ብሎም የቱሪዝም ገበያውን ለማገዝ ከፍተኛ ሚና ያለው በመሆኑ በቅርብ ጊዜ ተግባራዊ ለማድረግ እንደሚሰራ አንስተዋል።

የባሕር ዳር  ዩኒቨርሲቲ ጂኦስፓሻል ዳታ እና ቴክኖሎጂ ሴንተር (GDTC) ዳይሬክተር ዶ/ር ዳንኤል አያሌው በዩኒቨርሲቲው ከዚህ ቀደም የተሰሩ የከተማዋን የቱሪስት ፍሰት የሚያሳዩ መተግበሪያዎች እና ሌሎች የዲጂታል ጅማሮዎችን እና አቅሞች እንደ መነሻ በመውሰድ በፕሮጀክቱ ውጤታማ ስራ ለመስራት ዩኒቨርሲቲው በሙሉ አቅሙ እንደሚያግዝ አንስተዋል።

የስፔስ ሳይንስና ጂኦስፖሻል ኢንስቲትዩት የከተሞችን የዲጂታል አድራሻ ስርዓት ለመዘርጋት በያዝነው የበጀት አመት ለ6 ከተሞች ተግባራዊ ለማድረግ እየሰራ ሲሆን የቢሾፍቱ እና አዳማ ከተሞች በመጠናቀቅ ላይ ይገኛል።

@space science and Geo - Spatial Institute

 

የሳይንስ ኢንኩቤሽን ማዕከል (STEM) ለተማሪዎች ሲሰጥ የነበረውን የተግባር ተኮር ትምህርት አጠናቀቀ

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ፣ ነሐሴ 30/2014 (ባዳዩ-BDU) የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሳይንስ ኢንኩቤሽን ማዕከል /STEM/ በ2014 ዓ.ም የክረምት መርሃ-ግብር ከተለያዩ ትምህርት ቤቶች ለተወጣጡ ተማሪዎች ሲሰጥ የነበረውን የተግባር ተኮር ትምህርት አጠናቀቀ፡፡

ዩኒቨርሲቲው በሳይንስ ኢንኩቤሽን ማዕከል /STEM/ ከባሕር ዳር ከተማ ከሚገኙ የግል እና የመንግስት ትምህርት ቤቶች ከ5ኛ-10ኛ ክፍል ከሚገኙ ተማሪዎች ውስጥ በመመልመል በክረምቱ መርሃ-ግብር የተግባር ተኮር ትምህርት ሲያሰለጥናቸው የነበሩትን ተማሪዎች ስልጠናቸውን በማጠናቀቃቸው ሽኝት አድርጎላቸዋል፡፡

በማጠቃለያ መርሃ-ግብሩ ተገኝተው ንግግር ያደረጉት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የምር/ማህ/አገ/ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ተስፋዬ ሽፈራው ማዕከሉ ከ2004 ዓ.ም ጀምሮ በተለያዩ መስኮች ከ3,090 በላይ ተማሪዎችን በማሰልጠን አስተዋፆ እያረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ዶ/ር ተስፋዬ አክለውም ተማሪዎች የመማር ፍላጎታቸውን የሚጨምር መልካም ቆይታና ውጤታማ ጊዜ እንደነበራቸው አውስተው፣ የቀሰሙትን የፈጠራና የሳይንስ ግንዛቤ ለሌሎች በማካፈል የዩኒቨርሲቲው አምባሳደር እንዲሆኑ አደራ በመስጠት በክረምቱ የትምህርት ቆይታቸው ያካበቱትን ዕውቀት ወደ የት/ቤታቸው ሲመለሱ የተማሩትን ለሌሎች የክፍል ጓደኞቻቸው ማካፈል እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡

የሳይንስ ኢንኩቤሽን ማዕከሉ ም/ዳይሬክተር ዶ/ር አለሙ ተስፋየ በክረምቱ መርሃ-ግብር በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በምህንድስና እና ሂሳብ ትምህርቶች ለተማሪዎቹ በተግባር የተደገፈ ስልጠና መሰጠቱን በመግለጽ ስልጠናው ተማሪዎቹ ለራሳቸውም ሆነ ለአካባቢው ማህበረሰብ ችግር ፈቺ የፈጠራ ስራ እንዲሰሩና የፈጠራ ክህሎታቸውን እንዲያሳድጉ የሚረዳ እንደነበር አስረድተዋል፡፡

በተግባር ተኮር የትምህር ስልጠናውን ከተካፈሉ ተማሪዎች ውስጥ አብላጫ ውጤት ላመጡት እውቅና የመስጠት ፕሮግራም በእለቱ ተካሂዷል፡፡ በማዕከሉ Science Shared Camp, Summer Camp, Girls’ Camp, Project Work, Weekends, Lab Works የተሰኙ ፕሮግራሞች የሚሰጡ መሆኑም ታውቋል፡፡

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ-ባዳዩ-BDU

Description: 💦Description: 💦Description: 💦Description: 💧Description: 💦Description: 💦Description: 💧Description: 💦Description: 💦Description: 💦

ከዓባይ ጓዳ ጥበብ ሲቀዳ

Wisdom at the source of Blue Nile

Thank you for Inviting, like, share & visiting BDU page!

 

በሙሉጎጃም አንዱዓለም

የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሳይንስ ማበልፀጊያ ማዕከል (STEM Center) በየዓመቱ የሚያካሂደውን የልጃገረዶች የሳይንስ ካምፕ(STEM Girls Camp) ስልጠናና ውድድር በፔዳ ግቢ ለ8 ተከታታይ ቀናት ሲያካሂድ ከቆየ በኋላ ለአሸናፊዎች የተለያዩ ሽልማቶችን በማበርከት ፍፃሜውን አግኝቷል፡፡

በመዝጊያ ፕሮግራሙም የቀድሞው የዩኒቨርሲቲው ምርምርና ማህበረሰብ ም/ፕሬዘዳንት እና በአሁኑ ስአት ደግሞ የአብክመ የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ የሆኑት ዶ/ር ሙሉነሽ አበበን እና የከተማውን የትምህርት መምሪያ ም/ኃላፊ አቶ መላክ ጀመረን ጨምሮ  የዩኒቨርሲቲው ኢንፎርሜሽንና ስትራቴጂክ ኮምኒኬሽን ም/ፕሬዘዳንት ዶ/ር ዘውዱ እምሩ እና ሌሎች የዩኒቨርሲቲው መምህራን ተገኝተዋል፡፡

ዶ/ር ዘውዱ እምሩ በእግር ኳስ ጨዋታው ላሸነፉት ለፕሮፌሰር የአለምፀሀይና ለፕሮፌሰር ሶስና ቡድኖች ዋንጫ ከአበረከቱ በኋላ በመልዕክታቸው ተማሪዎች ወደ መጡበት ት/ቤት ሲመለሱ የቀሰሙትን እውቀት ለሌሎች የትምህርት አጋሮቻቸው እንዲያካፍሉና በያዙት ላይ ተጨማሪ እውቀት በመገብየት ለሞዴልነት የተጠቀሱትን ታዋቂ ሴት ሳይንቲስቶች በመተካት አገር ተረካቢ ትውልድ እንዲሆኑ አሳስበዋል፡፡

ዶ/ር ሙሉነሽ አበበ በበኩላቸው በአጠቃላይ ቆይታቸው የላቀ ውጤት ላስመዘገቡት ለዶ/ር ደብረወርቅ ቡድኖች የአንደኝነትን ማዕረግ የሚገልፀውን ዋንጫ አበርክተው በተማሪዎች መካከል የሚደረገው ፉክክር የወደፊት ታላቅነታቸውን እንደሚያሳይና ሳይንቲስቶችን እንደሚተኩ የሚያመላክት ነገር እንዳለ ጠቁመው ዕቅድ፣ጠንክሮ መስራትና ለሚያጋጥሙ ተግዳሮቶች በቁርጠኝነት መታገል ለከፍተኛ ደረጃ እንደሚያደርስ አስገንዝበዋል፡፡

አቶ መላክ የምስክር ወረቀት ለቡድን ተወካዮች ከሰጡ በኋላ እንደተናገሩት ዩኒቨርሲቲው እያበረከተ ያለውን ጉልህ አስተዋፅኦ አመስግነው ለወደፊቱም ድጋፉና ክትትሉ እንዳይለይ በማሳሰብ ቢሮአቸው ይህን የመሰሉ ትውልድ የመቅረፅ ስራዎች ላይ በጋራ የመስራት እቅድ እንዳለው ጠቁመዋል፡፡

በፕሮግራሙ ላይ በተማሪዎች መካከል የእግር ኳስ እና የዱላ ቅብብል ጨዋታ ውድድር፣ስነ ፅሁፍና የቆይታ ሪፖርት ቀርቦ የምስክር ወረቀትና ለአሸናፊ ቡድኖች የዋንጫ ሽልማት ስነ-ስርዓት ተከናውኗል፡፡

ተማሪዎች ፕሮግራሙ እጅግ በጣም ጥሩ መሆኑን ገልፀው ለሌሎች እድሉን ላላገኙት የክፍል ጓደኞቻቸው ተደራሽነቱ እንዲሰፋ እንዲሁም ቀጣይነት እንዲኖረው በአፅንኦት ተናግረዋል፡፡

የብር አዳማ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተመረቀ

ትዕግስት ዳዊት 

የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ኢን/ስት/ኮም ም/ፕረዚደንት ዶ/ር ዘውዱ እምሩ በምረቃ መርሃ ግብሩ ላይ እንደተናገሩት ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ መንግሥት ባወጣው የከፍተኛ ትምህርት አዋጅ ቁጥር 650 ለዩኒቨርስቲዎች ከተሰጣቸው ሦስት ተልዕኮዎች ውስጥ አንዱ የሆነውን በፍላጎት ላይ የተመሰረተ የማኅበረሰብ አገልግሎት መስጠት በተለያየ ደረጃ እየተገበረ ይገኛል፡፡ ይህ በእለቱ የተከናወነው የትምህርት ቤት ስራ ምረቃም የዙህ ጥረት አንድ አካል እንደሆነ ዶ/ር ዘውዱ ገልፀው ይህን መሰል ስራዎችም ሞዴል መደረግ በሚችሉበት ደረጃ እንደሚሰሩም ገልፀዋል፡፡ ዶ/ር ዘውዱ አክለውም ለትምህርት ቤቱ ግንባታ እውን እንዲሆን ከተለያዩ ባለሙያዎች እና የመንግስት ኃላፊዎች ትብብር ባሻገር ኤፍጂሲኤፍ (FGCF) የተሰኘው የግብረ ሰናይ ድርጅት ጉልህ ሚና ተጫውቷል ብለዋል፡፡ ይህም ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ በ2009 ዓ.ም. ግብረ ሰናይ ድርጅቱ ጋር በትምህርት ዘርፍ በትብብር ለመስራት ላደረጉት ስምምነት ተግባራዊ ማሳያ እንደሆነ ጨምረው ገልጸዋል፡፡ የኤፍጂሲኤፍ (FGCF) አማራ ክልል አስተባባሪ አቶ አቢወት አሸናፊ የተገነቡትን 16 መማሪያ ክፍሎች፣ አንድ አስተዳደር ሕንፃ ፣ አንድ ቤተ-ሙከራ እና አንድ ቤተ-መጻሕፍት በምረቃ መርሃግብሩ ለተገኙት አካላት ያስጎበኙ ሲሆን የህንጻውን ክፍሎች እንዲሁም ውስጣቸው ስላሉት ቁሳቁሶች እና ስለሚሰጡት አገልግሎቶች ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ አቶ አቢወት በቀጣይ ደግሞ በዋነኛነት የትምህርት ቤቱን ምድረ-ግቢ ማሳመር፣ ለመምህራን የተለያዩ አቅም ግንባታ ሥልጠናዎችን መስጠት እንዲሁም ለተማሪዎች የተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናዎችን ለመስጠት እንደታቀደ ገልፀዋል፡፡ የግንባታውን ወጪ ሶስት አካላት የሸፈኑት ሲሆን ባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ 30%፣ የአካባቢው ማኅበረሰብ እና ወረዳው 40%፣ እንዲሁም ኤፍጂሲኤፍ (FGCF) 30%ቱን አዋጥተዋል፡፡ በትምህር ቤቱ ምርቃት ላይ የተገኙት የቋሪት ወረዳ ትምህርት ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ የፀዳው አጥናፍ እንደተናገሩት ወረዳው በትምህርት ጥራት በኩል ሰፊ ችግር ያለበት በመሆኑ ይህ ግንባታ ሲገነባ ሰፊውን ችግር ለማቃለል የራሱ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ብለዋል፡፡ ተማሪዎች ከፈራረሰ ትምህርት ቤት ወጥተው ደረጃውን በጠበቀ ህንጻ እንዲማሩ በመደረጋቸው የትምህርት ጥራት እንደሚሻሻል ጠቁመው የተገነባውን ህንጻ ማህበረሰቡ እንደራሱ እንዲንከባከበው አሳስበው ለዚህ ህንጻ መገንባት አስተዋጽኦ ላደረጉት አካላት የአክብሮት ምስጋና አቅርበዋል፡፡ በመርሃግብሩ የተገኙት የተማሪ ወላጆች በበኩላቸው ትምህርት ቤቱ በ1972 ዓ.ም የተገነባ እንደነበረ ጠቁመው አሁን ላይ አገልግሎት ለመስጠት የማይችልበት ደረጃ ላይ እየደረሰ እያለ አዲሱ ህንጻ መገንባቱ ከሃሳብ እና ጭንቀት እንደታደገቸው ገልጸዋል፡፡ አክለውም አሁንም ያልተሟሉላቸው እነደ ውሀ እና መብራት ያሉ መሰረተ ልማቶች እንዲሟሉላቸው ጥያቄአቸውን አቅርበዋል፡፡ በመጨረሻም ወላጆች ልጆቻቸውን በርትተው እንደሚያስተምሩ ተናግረው ት/ቤቱን ወደ ሁለተኛ ደረጃ እንደሚያሳድጉትም ቃል ገብተዋል፡፡

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የሲቪልና የውሀ ምህንድስና ፋኩሊቲ 2ኛውን የአማራ ክልል የግብርና ፎረም “Small Scall Irrigation and Agricultural Technologies for Sustainable Development in Amhara Region” በሚል ርዕሰ ጥር 8/2010 ዓ/ም በባሕር ዳር ከተማ አካሂዷል።

በዚህ መርሀ ግብር ላይ ተገኝተው የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የአማራ ክልል አነስተኛና ጥቃቅን መስኖ ልማትና አቅም ግንባታ ድጋፍ ፕሮጀክት አስተባባሪ የሆኑት አቶ ማማሩ ጽድቁ ናቸው። እንደርሳቸው ገለጻ ይህ ፎረም የተቋቋመው በአማራ ክልል አነስተኛና ጥቃቅን መስኖ ልማት ላይ የሚታዩ የአቅም ክፍተቶችን ለማስወገድ፣ በግብርናው መስክ ላይ ሊኖሩ የሚችሉ እንከኖችን ለመለየትና የመፍትሄ አቅጣጫ በማስቀመጥ በክልሉ ላይ ምርትን ለመጨመር እንዲሁም ሞዴል የሰርቶ ማሳያ ቦታዎችን በማቋቋም የግብርና ሰርቶ ማሳያዎችን በመስራት ለማሳየትና በጉዳዩ ላይ የሚመለከታቸው መንግስታዊ እንዲሁም መንግስታዊ ያልሆኑ አጋር አካላት በጋራ ተናበው እንዲሰሩ ለማድረግ እንደሆነ ተናግረዋል። በአማራ ክልል በመስኖ ልማት ላይ በተለይም መስኖና ኢነርጂ፣ ግብርና ቢሮ፣ አውስኮድ፣ አመልድ፣ የአማራ ዲዛይንና ቁጥጥር እንዲሁም የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የተለያዩ ስራዎችን እየሰሩ እንደሆነና በተለይ የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከኖርዌይ መንግስት ጋር በመተባበር በክልሉ ላይ የተለያዩ የምርምር ስራዎች ሲያካሂድ እንደቆየና ፎረሙም ከተቋቋመ ጊዜ ጀምሮ የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነ እንደሆነና 2ኛውን የአማራ ክልል የግብርና ፎረም እንዳዘጋጀ ገልጸዋል።
የአማራ ክልል በተፈጥሮ ሀብት የታደለና በተለይም ለግብርና ስራ አመች እንደሆነ የገለጹት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ምክትል ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር የሆኑት ዶ/ር ዜና ማርቆስ ባንቴ ናቸው። አክለውም የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት በክልሉ ላይ የተለያዩ የምርምር ስራዎች እየሰራ እንደሆነና በመስኖ ልማት እንዲሁም አነስተኛና ጥቃቅን መስኖ ልማት ላይ ትልቅ ትኩረት በመስጠት እየሰራ እንደሆነና በተለይም በክልሉ ላይ የማህበረሰቡን ችግር የሚቀርፉ ምርምር በማካሄድ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ስራ መስራት እንደሚያስፈልግና በዘርፉ ያሉ ችግሮችን ለመቅረፍ እየተሰራ እንደሆነ ገልጸው በዚህ ጉባኤ ላይም በክልሉ ውስጥ አነስተኛና ጥቃቅን መስኖ ልማት ስራዎች እንዴት መሰራት እንዳለበትና በዘርፉ የሚታዩትን ችግሮች በመለየት የመፍትሄ አቅጣጫ ማስቀመጥ አስፈላጊ እንደሆነ ጠቁመው በቴክኖሎጂ ፈጠራ እና በአነስተኛና ጥቃቅን መስኖ ልማት ስራዎች ላይ የራሱን ድጋፍ እንደሚያደርግና በምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ስራዎች ማህበረሰቡን የሚጠቅሙ ቴክኖሎጂዎችን በማፍለቅ ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

ግብርና የግብርና ባለሙያዎችን ብቻ የሚመለከት ጉዳይ ሳይሆን የተለያዩ የሙያ መስኮችን የሚመለከትና የሚዳስስ ጉዳ እንደሆነ የተናገሩት የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የሲቪልና የውሀ ምህንድስና መምህርና ተመራማሪ እንዲሁም የፎረሙ አስተባባሪ የሆኑት ዶ/ር ሰይፉ አድማሱ ናቸው። አክለውም በዚህ ፎረም ላይ ለአርሶ አደሮች የሚጠቅሙ ጉዳዮች ምንድን ናቸው? ብሎ በመለየትና የክልሉን ህዝብ የሚጠቅሙ ስራዎችን ለመስራትና ምን እየተካሄደ ነው? ምን አይነት ጥረቶች አሉ? ማን ማን ጉዳዩ ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው? ምን አይነት ሀሳቦች አሉ? የሚለውን ለመገንዘብ እና ፖሊሲ አውጭዎችና አስተግባሪዎች እንዲሁም የሚመለከታቸው አጋር አካላት ከዚህ ውይይት ላይ ግንዛቤ በመውሰድ እንዲሰሩና የጋራ ግንኙነታቸውን እንዲያሰፉ ለማድረግ እንደሚያግዝም አስተባባሪው ተናግረዋል።

በBDU-NORHED ኘሮጀክት ጽ/ቤት አስተባባሪነት በትምህርትና ስነ ባሕርይ ኮሌጅ ፣ በባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ ሳይንስ ማልፀጊያ ማዕከል አና በFGCF ትብብር ከአማራ ክልል አራት ዞኖች (ምዕራብ ጎጃም፣ምስራቅ ጎጃም፣ ደቡብ ጎንደር እና አዊ) ከሚገኙ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለተውጣጡ 100 መምህራን የዘጠኝ ቀናት ስልጠና ተሰጠ፡፡

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የፔዳጐጅና ትምህርት ምርምር ተቋም ዳይሬክተርና የBDU-NORHED ኘሮጀክት አስተባባሪ ዶ/ር ዳዊት አስራት ስልጠናው በመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት በተለይም የሳይንስና የሂሣብ ትምህርቶች ላይ ተማሪዎች ፅንሰ ሀሣቦችን በቀላሉ እንዲገነዘቡ ለማድረግ የሚረዱ መንገዶችን ማስተማርን ዓላማ ያደረገ ነው ብለዋል፡፡ የትምህርት ጥራትን ማስጠበቅ የእያንዳንዱ ባለሙያ ግዴታ መሆኑና የዚህ እንቅስቃሴ አንድ አካል ሊሆን የሚችለው ደግሞ የመምህራንን አቅም ማጎልበት እንደሆነ ዶ/ር ዳዊት ገልፀዋል፡፡
ዶ/ር ዳዊት አክለውም የአጭር ጊዜ ስልጠናው ትኩረት ያደረገው በአምስት ጉዳዮች ማለትም በሂሳብ እና ሳይንስ ትምህርት ስነ-ዘዴ፣ በተግባራዊ ምርምር፣ ስርዓተ-ፆታን መዕከል ያደረገ የማስተማር ዘዴ እና በልይይት ማስተማር እና ምዘና ላይ ነው ብለዋል፡፡

በስልጠናው ተሳታፊ የነበሩ መምህራን ስልጠናው ከዕለት ተዕለት የማስተማር ስራቸው ጋር በቀጥታ የሚገናኙና በቀላልና ከአካባቢ የሚገኙ ቁሳቁሶችን ተጠቅመው በሚሰሯቸው ሙከራዎች ተማሪዎች የሳይንስና የሂሳብ ፅንሰ ሃሳቦችን በቀላሉ ለመገንዘብ እንዲችሉ የሚያግዙ መንገዶችን የተማሩበት መሆኑን ገልፀዋል፡፡

የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮን ወክለው በስልጠናው የተገኙት አቶ ልሳነወርቅ ፋንታሁን ዩኒቨርስቲው ተነሳሽነቱን ወስዶ ስልጠናውን መስጠቱን አመስግነው ሰልጣኞችም በስልጠናው ያገኙትን እውቀት በስራ ላይ በማዋል ለትምህርት ጥራት መሻሻል የራሳቸውን ድርሻ እንዲወጡ አሳስበው የክልሉ ትምህርት ቢሮውም በመሰል ጉዳዮች ላይ ወደፊት ከዩኒቨርስቲው ጋር ተባብሮ ለመስራት ዝግጁ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡

በመጨረሻም የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ም/ኘሬዚዳንት ዶ/ር ሙሉነሽ አበበ እና በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ የስርዓተ ትምህርት ዝግጅትና ትግበራ ዳይሬክተር አቶ ሙላው አበበ ለስልጠናው ተሳታፊዎች ሰርተፊኬት የሰጡ ሲሆን ዶ/ር ሙሉነሽ በመዝጊያ ንግግራቸው የሁሉም ሙያ መነሻው መምህርነት ትልቅ ፀጋ መሆኑን ገልፀው ሰልጣኝች በስልጠና ቆይታቸው ያገኙትን እዉቀት ወደ መሬት አውርደው ተግባራዊ እንዲያደርጉት አሳስበዋል፡፡

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የአደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ጥናት ተቋም ለተቋሙ ተማሪዎች፣ መምህራንና የአስተዳደር ሰራተኞች ሰኔ 15 እና 16 2009 ዓ.ም የመጀመሪያ የህክምና እርዳታ አሰጣጥ ስልጠና በግብርናና አካባቢ ሳይንስ ኮሌጅ ግቢ ሰጠ፡፡ የአደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ጥናት ተቋም ዋና ዓላማው አድርጐ እየሰራ ያለው መማር ማስተማር፣ ምርምር እና የማህበረሰብ አገልግሎት እንደሆነ እና ይህ የመጀመሪያ የህክምና እርዳታ ስልጠናም የማህበረሰብ አገልግሎት አንዱ አካል መሆኑን እና ስልጠናው አዳጋ ሲደርስ በመጀመሪያዎቹ ደቂቃዎች የሚከሰት ጉዳትን መቀነስ እንዲቻል ታስቦ የተሰጠ እንደሆነ የተቋም መምህርና የስልጠናው አስተባባሪ አቶ ታረቀኝ አያሌው ገልፀዋል፡፡ ​አስተባባሪው አክለውም በዩኒቨርሲቲውም ሆነ ከውጭ ማህበረሰብ ዘንድ የመጀመሪያ የህክምና እርዳታ እንዴት እንደሚሰጥ ግንዛቤ ባለመኖሩ የተለያዩ ችግሮች እንደሚፈጠሩ እና ክብር የሆነው የሰው ልጅ ህይወት ለህልፈተ ሞት እንደሚዳረግ ገልፀው ስልጠናው ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል የመጡ ተማሪዎች ጨምሮ ያካተተ በመሆኑ ከራሳቸው አልፎ ለቤተሰቦቻቸው እንዲሁም ለማህበረሰቡ ግንዛቤ ለመፍጠር እንደሚያግዝና በቀላሉ ተደራሽ እንደሚሆን ተናግረዋል፡፡ ሰልጣኞችም የተሰጣቸውን ስልጠና ወደ ተግባር ከመቀየር ባሻገር ለማህበረሰቡ ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ግንዛቤ የመፍጠር ሥራ እንዲሰሩ አስተባባሪው ጨምረው አሳስበዋል፡፡ በአደጋ ጊዜ የሚከሰት ሞትን በመጀመሪያ እርዳታ ህክምና ከ 40 እስከ 60% መቀነስ እንደሚቻል ነገር ግን ይህ ግንዛቤ በሀገራችን አደጋ በሚከሰትበት ቦታ በፍጥነት የሚገኙትን የመከላከያ ሰራዊት እና የፖሊስ አካላት ጨምሮ ዝቅተኛ እንደሆነ በአደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ጥናት ተቋም መምህር እና የስልጠናው ተሳታፊ አቶ አለበል አይናለም ገልፀዋል፡፡ አቶ አለበል አክለውም የመጀመሪያ ህክምና እርዳታ ለመስጠት ትምህርቱን ብቻ መማር በቂ እንዳልሆነ እና ከውስጥ የሚመነጭ ፍላጐት እንዲሁም በፍቃደኝነት ላይ የተመሰረተ መሆን እንዳለበት ጠቁመው የትምህርት ክፍሉ ወደፊት ከዩኒቨርሲቲው እና ከአካባቢው ማህበረሰብ እንዲሁም ከቀይ መስቀል ጋር በመሆን ግንዛቤ ለመፍጠር መሰራት እንደሚገባው አሳስበዋል፡፡

ኢትዮጵያ በእንስሳት ሃብት ከአፍሪካ ሀገሮች የተሻለ ደረጃ ላይ ብትገኝም በእንስሳት መኖ እጥረት ምክንያት ማግኘት የሚገባትን ጥቅም እያገኘች እንዳልሆነ የተለያዩ የመረጃ ምንጮች ያስረዳሉ፡፡ ከዚህ ችግር አኳያ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት የተለያዩ የንጥረ ነገር ውህዶችን በመጠቀም የፅንሰ-ሃሳብና የተግባር ስልጠና ለተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች በግብርናና አካባቢ ሣይንስ ኮሌጅ ግቢ ቤተ-ሙከራ ለ7 ተከታታይ ቀናት ሰጥቷል፡፡

የማዕከሉ ዳይሬክተር ዶ/ር የሻምበል መኩሪያው ቴክኖሎጅን በመጠቀም ማንኛውም ማህበረሰብ በቀላሉ አረንጓዴ የእንስሳት መኖ በአጭር ጊዜ፣ በአነስተኛ ጉልበትና ውሃ በርካታ የእንስሳት መኖ በማዘጋጀት መጠቀም የሚቻልበትን ዘዴ ለማሳወቅ ስልጠናው ፈር ቀዳጅ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ ለቴክኖሎጂው ዋና ግብዓት የሆነውን ውህድ በዩኒቨርሲቲው የኬሚስትሪ ት/ክፍል ሙሁራን ተሰርቶ የቀረበ መሆኑንም ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡ ከGIZ የእንስሳት ሃብት ልማት ማስፋፊያ ኤጀንሲ የመጡት አሰልጣኝ አቶ ኃይለየሱስ አባተ የቴክኖሎጂውን ግኝትና አዋጭነት ሲገለፁ ዘርፈ ብዙ ፋይዳ እንዳለው፣ በተለይ ዝናብ አጠርና ድርቅ በሚያጠቃቸው ቦታዎች አካባቢ በስፋት መሰራት እንደሚቻል፣ በ7 ቀናት ውስጥ ከ25-30 ሴንቲ ሜትር ርዝመት ያለው አረንጓዴ መኖ ማድረስ እንደሚቻል እንዲሁም ከ 1 ኪሎ ግራም ገብስ ከ6-10 ኪሎ ግራም የሚመዝን የእንስሳት መኖ በቀላሉ ማግኘት እንደሚቻል ተናግረዋል፡፡ አሰልጣኙ አያይዘውም መኖው በተለይ ለእንቁላል ጣይ ዶሮዎች የንጥረ ነገሩ ውህድ ከፍተኛ ፕሮቲን ስላለው በርካታ እንቁላል የመጣል አቅማቸውን እንደሚያጐለብትና ስልጠናው ከሙከራ እስከ ትግበራ መሰጠቱን አስገንዝበዋል፡፡ ሰልጣኞች በባሕር ደር ከተማ የተደራጁ ሥራ አጥ ወጣቶች፣ የኮሌጁ የእንስሳት እርባታ ሠራተኞች እንዲሁም የዩኒቨርሲቲውን መምህራንና የድህረ ምረቃ ተማሪዎች ሲሆኑ ከስልጠናው ከፍተኛ ግንዛቤ እንደጨበጡና በቆይታቸው መኖው ለእንስሳት መቅረብ መቻሉን ብሎም የኮሌጁ ላሞችና በጐች ሲመገቡት ማስተዋላቸውን ተናግረዋል፡፡

Pages