ቃጠሎው በቁጥጥር ስር ውሏል

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ (ፔዳ) ትናንት ምሽት በፖሊ-ፔዳ ኢንተርፕራይዝ ላይ ቃጠሎ ተከስቶ በተደረገ ከፍተኛ ርብርብ ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡

 

ቃጠሎውን ለማጥፋት የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች፣ መምህራን፣ የባሕር ዳር ከተማ ወጣቶች፣ የጸጥታ ሃይልና ልዩ ኃይል አባላት እንዲሁም የአካባቢው ማህበረሰብና የእሳት አደጋ መከላከያ ባደረጉት ያላሰለሰ ጥረት ቃጠሎው የከፋ ጉዳት ሳያደርስ መቆጣጠር የቻሉ ሲሆን ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ለእነዚህ በባለቤትነት ስሜት ከፊት ተሰልፈው ቃጠሎውን ለመቆጣጠር ለተረባረቡት አካላት እጅግ ከፍተኛ ምስጋና አቅርቧል፡፡

 

የኢንፎርሜሽንና ስትራቴጂክ ኮሚኒኬሽን ም/ፕሬዚዳንት ጽ/ቤ

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ