የችግኝ ተከላ

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አምስት የትምህርት ተቋማት የችግኝ ተከላ አካሄዱ

በምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት አስተባባሪነት በሶሻል ሳይንስ እና ሂውማኒቲስ ፋኩልቲዎች እንዲሁም ፣ በትምህርትና ስነ ባህሪ ፣ ሳይንስ እና በቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጆች  የሚገኙ መምህራንና ሰራተኞች በቤዛዊት ተራራ የችግኝ ተከላ አካሄዱ፡፡

በመርሃ ግብሩ የሶሳይቲ ፎር ኢኮ ቱሪዝም እና ባዮዳይቨርሲቲ ኮንሰርቬሽን በጎ አድራጎት ሲቪል ማህበር ስራ አስኪሂያጅ ትዝታ የኔአለም እንዳሉት እየለማ ያለው እና በእለቱ ችግኝ የተተከለበት ቦታ ከባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጋር በ225 ሄክታር  መሬት የላንታና  ካማራ አረምን ማስወገድ እና መልሶ ማልማት የ5 ዓመት ፕሮጀክት እየተካሄደበት የሚገኝበት አካባቢ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ አያይዘውም ችግኞቹ አገር በቀል የሆኑ እና ሌሎችም የተካተቱበት ሲሆን በየእለቱ ችግኞችን የሚንከባከቡ ጊዚያዊ ሰራተኞች እንዳሉ ገልፀዋል ፡፡ 

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሀገራችን የያዘችውን የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ የመትከል ሰፊ እቅድ ተከትሎ በተለያዩ ቦታዎችና ቀናት በ2012 ዓ.ም. ከፍተኛ አመራሮችንና መላውን የዩኒቨርሲቲውን እና በአማራ ክልል የሚገኙ የዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራሮችንም ያሳተፈ ችግኝ የመትከል  መርሃ ግብር እንዳካሄደ ይታወቃል፡፡