ግብርና እና አካባቢ ሳይንስ ኮሌጅ ዓመታዊ የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ

የግብርና እና አካባቢ ሳይንስ ኮሌጅ ዓመታዊ የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ አካሄደ
**************************************************************
የዘንዘልማ ግቢ የአስተዳደር ዘርፍ፡- የጠቅላላ አገልግሎት ፣ የተማሪ አገልግሎት፣ የሰው ሃብት አስተዳደር ፣ የግዥና ፋይናንስ አገልግሎት፣ የንብረት አስተዳደር፣ የፀጥታና ደህንነት ክፍሎች ስራቸውን በማቅረብ ዓመታዊ የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ አካሄዱ፡፡
በመርሃ ግብሩ የግብርና እና አካባቢ ሳይንስ ኮሌጅ ማኔጅንግ ዳይሬክተር አቶ ታደሰ መኳንንት የዕለቱን ዝርዝር ፕሮግራም ያቀረቡ ሲሆን ግምገማው ለቀጣይ በጀት ዓመት የተሻለ ለመንቀሳቀስ እንደመነሻ የሚሆኑ ሀሳቦችን ለማግኘት እና የነገ እቅድን በተሻለ ለመፈፀም ጉልህ ድርሻ እንደሚኖረው እምነታቸውን ተናግረዋል፡፡

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የአስተዳደር ጉዳዮች ኤክስኪዩቲቨ ዳይሬክተር አቶ ገደፋው ሽፈራው በበኩላቸው ሁሉም የስራ ክፍሎች በያዙት ዕቅድ መሰረት ምን ያህል ስራዎችን እያከናወኑ መሆኑን መገምገማቸው ለቀጣይ በጀት ዓመት ጠቃሚ ግብዓቶችን ከማግኘት ባሻገር በሌሎች ግቢዎች ባልተለመደ መልኩ መቅረቡ ይበል የሚያስብል መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በዋናነት ከተሳታፊዎች ለተነሱ የግቢው የውሃ እና የመብራት ችግርም ዩኒቨርሲቲው ሰባት አሚት ላይ በከፍተኛ ወጭ 5 ጉድጓዶች አስቆፍሮ በሶስቱ ጉድጓድ ላይ ውጤት እያመጣ ስለሆነ በቅርቡ ይፈታል ሲሉ ተናግረዋል፡፡
በመጨረሻም የግብርና እና አካባቢ ሳይንስ ኮሌጅ ዲን ዶ/ር አሳምነው ጣሰው በተገኙበት የተሻለ ስራ አፈፃፀም ላስመዘገቡ የኮሌጁ ሰራተኞች የእውቅና የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል፡፡