MoU Signed

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ከሃኪም ወርቅነህ መላኩ በያን ሶሳይቲ ጋር በጋራ ለመስራት የስምምነት ሰነድ ተፈራረመ
****************************************************************************************
በሙሉጎጃምአንዱዓለም
የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ኮሌጁ ከሃኪም ወርቅነህ-መላኩበያን ሶሳይቲ ከተባለው በአሜሪካን ሃገር ተቀማጭነቱን ካደረገው የትውልደ ኢትዮጵያዊያን ሃኪሞች ማህበር ጋር በጋራ ለመስራት የስምምነት ሰነድ ተፈራረመ፡፡

ስምምነቱን የተፈራረሙት የኮሌጁ የአካዳሚክና ምርምር ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መለሰ ገበየሁ እና የሶሳይቱ ተወካይ ዶ/ር ጌታቸው ፈለቀ ናቸው፡፡ በመርሃ-ግብሩ ላይ ሃኪም ወርቅነህ እና የህክምናው አባት ፕሮፌሰር እደማርያም ፀጋን በህክምናው ዘርፍ ያበከከቱትን ጉልህ አስተዋፅኦ በሰፊው ተወስቶ ለወደፊት በህክምናው ሙያ የላቀ ውጤት አስመዝግበው ለሚመረቁ ተማሪዎች በፕሮፌሰር እደማርያም ስም ሽልማት እንደሚዘጋጅ በውይይቱ ስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡ በተጨማሪም ለተመረጡ ተማሪዎች ለትምህርታቸው የሚሆን የገንዘብ ድጋፍ እንደሚሰጥ ስምምነት ላይ እንደተደረሰ ታውቋል፡፡