እየታጠበ በተደጋጋሚ መጠቀም የሚቻልበት የሴቶች የንጽህና መጠበቂያ(Reusable sanitary Pads) አዘገጃጀት ላይ ስልጠና ተሰጠ

የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ከዩኒሴፍ አማራ ፕሮግራም ጋር በመተባበር በአማራ ክልል ባሉ 4 ወረዳዎች ባለፈው ዓመት 80 ለሚሆኑ ሰዎች ታጥቦ በድጋሚ መጠቀም የሚቻልበት የሴቶች የንጽህና መጠበቂያ(ሞዴስ) አዘገጃጀትና አጠቃቀም ላይ ስልጠና የሰጠ መሆኑ ይታወሳል፡፡
አሁንም ለሁለተኛ ጊዜ ከጥቅምት 22-25/2010 ዓ.ም ከአራቱ ወረዳዎች አንዱ በሆነው በጎንደር ዙሪያ ወረዳ ማክሰኝት ከተማ ለ20 ሰልጣኞች ስለ ፓዱ ሙያዊ አዘገጃጀት በጨርቃጨርቅ ባለሙያ፤ጤና ላይ መደረግ ስላለበት ጥንቃቄ በጤና ባለሙያና ፓዱን አምርተው እንዴት ትርፋማና ውጤታማ መሆን እንደሚችሉ በቢዝነስ ባለሙያዎች በዩነቨርሲቲው የኢንትረፕርነርሽፕ ልማትና ማበልጸጊያ ማዕከል አስተባባሪነት ስልጠናው ተሰጥቷል፡፡