Internal vacancy announcement

ቀን፡ 19/07/2011 ዓ.ም

የውስጥ የስራ ማስታወቂያ

==============

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ባወጣው አዲስ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አመራሮች መመደቢያ መመሪያ መሰረት ብቁ አመልካቾችን ከዩኒቨርሰቲው አወዳድሮ ለእንስሳት ሳይንስ እና እንስሳት ህክምና ዳይሬክተር  መቅጠር ይፈልጋል፡፡

 

የማወዳደሪያ መስፈርት

1ኛ. የትምህርት ደረጃ፡ ሌክቸረርና ከዚያ በላይ ያለው/ያላት

2ኛ. በከፍተኛ ትምህርት ተቋም፣ በኢንዱስትሪ፣ በምርምር ተቋማት ወይም መሰል ተልዕኮ ባላቸው ተቋማት በልዩ ልዩ ኃላፊነት ዕርከን ያገለገለ/ችና ጉልህ አስተዋጽኦ ያበረከተ/ች፤

 

3ኛ. በሚያመለክቱበት አካዳሚክ ክፍልና ዘርፍ ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ ባገናዘበ መልኩ የከፍተኛ ትምህርት ተደራሽነት፣ ፍትኃዊነት፣ ጥራት፣ ተገቢነትና ዓለምአቀፋዊነትን ለማሳካት፣ አካዳሚክ ክፍሉን የልህቀት ማዕከል ለማድረግ፣ ተጨማሪ ሀብት ለማስገኘት፣ እንዲሁም ዓለማቀፋዊና አገራዊ ጉድኝቶችን ለመፍጠርና ለማስፋት በሚደረገው ሂደት አስተዋጽኦ ለማበርከት የሚያስችል ስትራቴጂያዊ ዕቅድ ማዘጋጀትና ማብራሪያ መስጠት የሚችል/ምትችል፤

 

4ኛ. የአካዳሚክ ክፍሉ ማህበረሰብ፣ የአካዳሚክ ኮሚሽኑ አባላት እንዲሁም የሚመለከታቸው ተጋብዘው በሚገኙበት መድረክ በአጀንዳዎች ላይ በአካል

ተገኝቶ/ታ ማብራሪያና ገለጻ መስጠት የሚችል/ምትችል፤

 

አመልካቾች፡-

ይህ ማስታወቂያ በዩኒቨርሰቲው የማስታወቂያ ሰሌዳና ድህረ-ገጽ ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ ቀናት የትምህርትና የስራ ልምዳቸውን ማስረጃ ፎቶ ኮፒ እንዲሁም ያዘጋጁትን ከአምስት ገጽ ያልበለጠ ስትራቴጅያዊ ዕቅድ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡

 

ለበለጠ መረጃ በሚከተሉት ስልክ ቁጥሮች +251 58 226 3210/+ 251 918 35 3494 ደውሎ ማነጋገር ይቻላል