-
R- Software
Statistics Department Computer Lab & Mathematics Department Computer LabMon, 06/26/2017 to Fri, 06/30/2017
-
SPSS
Statistics Department Computer Lab & Mathematics Department Computer LabMon, 06/26/2017 to Fri, 06/30/2017
-
Qualitative Research Methods
Capacity Building Training HallTue, 06/27/2017 to Fri, 06/30/2017
ለፔዳ ግቢና ለቢዝነስና ኢኮኖሚክሰ ኮሌጅ አስተዳደር ሰራተኞች ስልጠና ተሰጠ
የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ የስልጠና ዳይሬክቶሬት ከፔዳ ግቢ ማኔጅንግ ዳይሬክተርና ከቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ ማኔጅንግ ዳይሬክተር ጋር በመተባበር በሁለቱም ግቢዎች በተዘጋጀዉ አዳራሽ ላይ በደንበኞች አያያዝና ስነምግባር ዙርያ ከቢዚነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ በመጡ አሰልጣኞች ከ23-24/11/2011 ዓ/ም ድረስ ለ 110 ሰልጣኞች ስልጠና ተሰጧቸዋል፡፡ በዚህም ስልጠና ተሳታፊዎች ከስልጠናዉ ሰፊ ዕዉቀት እንዳገኙና ራሳችንንም እንድንፈትሽና እንድናይ ያደረገን በመሆኑ ለቀጣይ ስራችን ከፍተኛ መነሳሳትን ፈጥሮልናል ፡ነገር ግን በዚህ ስልጠና ላይ ሁሉም የዩንቨርሲቲዉ ማህበረሰብ በተለይ የበላይ አመራሮች ስልጠናዉን ቢወስዱ የተሸለ ስራ ይሰራል ብለን እናምናለን በማለት ገልጸዋል፡፡ በመጨረሻም የዩኒቨርሲቲዉ የስልጠና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ሆኑት አቶ ወርቁ አበበ ይህ ስልጠና ለእናንተ ብቻ ሳይሆን ለዩኒቨርሲቲዉ ለሁሉም ማህበረሰብ በተከታታይነት የሚሰጥ ይሆናል ፡፡ ስለሆነም እናንተም በሰለጠናችሁበት አግባብ የደንበኛን ክቡርነት በመገንዘብ ከስልጠናዉ በቀሰማችሁት ዕዉቀት መሰረት የአገልጋይነት ወኔን በመላበስ ተግታችሁ እንድትሰሩ እያሳሰብኩ ቀጣይም ወደ ስራ ክፍላችሁ ዳይሬክቶሬቱ በመንቀሳቀስ የስልጠናዉን አፈጻጸም የሚከታተል መሆኑን በመግለጽ ስልጠናዉ ተጠናቋል፡፡